የሀዋሳ ከተማ ባህል ኪነት ቡድን
የሀዋሳ ከተማ ባህል ኪነት ቡድን የተመሰረተው በ2004 ዓ.ም ሲሆን የቡድኑ አባላት 22 ናቸዉ፡፡ ኪነት ቡድኑ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የሲዳማንና የተለያዩ ብሄሮች ሙዚቃዎች እያስተዋወቀና ታዳሚዎችን እያዝናና የቆየ ሲሆን ለከተማዉ የባህል ሙዚቃ ዕድገት የራሱን አበርክቶ እያደረገ ይገኛል፡፡ ኪነት ቡድኑ በሲዳማና በሌሎች ባህላዊ ሙዚቃዎችና ስነ-ጥበባዊ ክዋኔዎች ልምዱን እያዳበረ ለጉብኝት ወደ ከተማችን ለሚመጡ እንግዶች ከማዝናናት አልፎ የብሔሩን ባህላዊ ጭፈራዎችና አለባበሶችን እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ የኪነት ቡድኑ የሲዳማ ብሄር ቱባ ባህሎች ማለትም ፋሮ፤ ሃኖ፤ ሆሬ፤ ቄጣላና ሌሎች ባህላዊ ውዝዋዜዎችን ለጎብኝዎችና ታዳሚዎች በማስተዋወቅም ነው ሚናውን እየተወጣ የሚገኘው፡፡