Skip to main content

                              ባህላዊ አልባሳት

ሌላው በሀዋሳ ከተማ ባህላዊ አልባሳትን አዘጋጅተዉ ለገቢያ የሚያቀርቡ ማህበራትና ግለሰቦች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም በባህል ልብስ ስራዎች ላይ የተሰማሩ ለከተማዉ ባህላዊ አልባሳትና ለቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡

ማህበራቱ የሲዳማን ቱባ ባህል የሚያንፀባርቁና የተለያዩ ብሄር ብሄረቦች አልባሳትን በማዘጋጀት ባህልን ከማስተዋወቅ አልፈዉ ለከተማዉ ገቢ ዕድገትና በስራ ዕድል ፈጠራ የራሳቸውን አሻራ እያኖሩ ይገኛሉ፡፡ በእነዚህ ተቋማት የሚዘጋጁ የሲዳማ ባህላዊ አልባሳትን ለመጠቀስ ያክልም ጎንፋ፣ ጎርፋ፣ ቆሎ፣ ወዳሬ እና ላሴ የሚባሉ ሲሆን አልባሳቱ የቱሪስቶችን ቀልብ በመሳብ በጎብኝዎች እና በከተማዋ ነዋሪዎች ልዩ ትኩረት ማግኘት የቻሉም ናቸው፡፡ ይህ ዘርፍ የባህል ቱሪዝምን ከማሳደግ ባለፈ ለብዙ ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ለከተማዉ ወጣቶች ኢኮኖማዊ ተጠቃሚነት ሚናዉን እየተወጣ ይገኛል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጎብኝዎች ወደ ሀዋሳ ሲመጡ እነዚህን ባህላዊ አልባሳት ገዝተው ሲደምቁ መመልከት እየተለመደ መጥቷል፡፡

b